ግንቦት ፴swriof0n Gg p 1oah(19Vet0ci
ግንቦት ፴ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፸ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፺፮ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፭ ቀናት ይቀራሉ።
ማውጫ
- 1 ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- 2 ልደት
- 3 ዕለተ ሞት
- 4 ዋቢ ምንጮች
ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፰፻፴፮ ዓ/ም - የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር፣ ወ. ወ. ክ. ማ. (YMCA) በሎንዶን ተመሠረተ።
- ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - ከዓረብ ባሕር ላይ የተነሳ ታላቅ አውሎ ነፋስ ያስከሰተው ማዕበል ከመቶ ሺ በላይ የሚቆጠሩ የቦምቤይ (የአሁኗ ሙምባይ) ከተማ ነዋሪዎችን ሕይወት አጥፍቷል።
- ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - አዲስ ዘመን በሚለው መጠሪያ የሚታወቀው ብሔራዊ ጋዜጣ በይፋ ሥራ ጀመረ። የጋዜጣው ሥያሜ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት ሲገቡ «ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የአዲስ ዘመን መጀመሪያ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል።
ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፯፻፲፭ ዓ/ም - በዓለም የታወቀው የምጣኔ ሀብት ጥናት ሊቅ፤ የስኮትላንድ ተወላጁ አዳም ስሚዝ (Adam Smith) በዚህ ዕለት ተወለደ።
ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፭፻፴ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ካሌብ አረፉ።
ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- (እንግሊዝኛ) http://en.wikipedia.org/wiki/June_7
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |
![]() |
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! | ![]() |